የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና በልሳን መናገር ግንኙነት አላቸውን?

Описание к видео የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና በልሳን መናገር ግንኙነት አላቸውን?

የዚህ፥ 'የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና በልሳን መናገር ግንኙነት አላቸውን?' የሚለው ትምህርት ዋና አሳብ ይህ ነው፤ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ተግባር አማኝን ከአካሉ፥ ከክርስቶስ አካል፥ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ማቆራኘት ነው።

መቼ ነው አንድ ሰው የክርስቶስ አካል ክፍል የሚሆነው? ሲያምን። የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በሙሉ በመንፈስ ተጠምቀው ነበር? በእርግጥ ተጠምቀዋል። ሁሉስ በልሳኖች ይናገሩ ነበር? አይናገሩም። ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅና በልሳኖች መናገር ይቆራኛሉ? የለም፤ አይቆራኙም።

ልክ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ልሳኖች ቁርኝት እንደሌላቸው ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳኖችም ቁርኝት የላቸውም። የመንፈስ ጥምቀት አንድ ሰው ክርስቲያን ሲሆን፥ ዳግም ሲወለድ ወደ ክርስቶስ አካል የሚገባበት ሥርዓት ነው።

የቃሉን ትምህርት በሰውኛ ልምምድ እየሸቃቀጥን ቃሉን ትተን ልምምዶችን ማስተማርና ማለማመድ የለብንም። ቃሉን እንማር፤ ቃሉን እናስተምር፤ ቃሉን እንታዘዝ። ይህንን እንድናደርግ መንፈስ ቅዱስ ራሱ ይርዳን።

Комментарии

Информация по комментариям в разработке