የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ ግጥም መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ቴዎድሮስ በለጠ ዜማ ዲ/ን ዘላለም ታከለ (ዘጎላ)

Описание к видео የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ ግጥም መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ቴዎድሮስ በለጠ ዜማ ዲ/ን ዘላለም ታከለ (ዘጎላ)

🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ
~~~~~~~~~~~~~~~

ምነው እሱን በሆንኩ
ያን የቀኝ ወንበዴ
ብመስለው ላ’ንድቀን : ባየው መንገዴ

ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት
አልያም ለመዝረፍ ሕይወትን ለማጥፋት

በዚያ መንገድማ

ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና
እኔን ታውቀኝ የለ … 
የወንበዴ አለቃ ያ’ጢኣተኞች ዋና

ያ … ጸጸት ያዘለ
በዚያች የጭንቅ ሠዓት «አስበኝ» እያለ
ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ
ካ’ዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ

እኔም እንደ ጥጦስ : ማታዬ እንዲያምር
ብትለኝ ምን አለ? …
«ከገነት ተጠለል: ዛሬን ከእኔ እደር»


🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ : ዛሬን ከእኔ እደር»




ደ’ሞ ይህን ተመኘሁ
ለንጊኖስን በሆንኩ
ያቺን ዕለተ ዓርብ : ቀራንዮ በዋልኩ

ለአመጽ አይደለም : ከከአይሁድ ለማበር
አልያም ለመውጋት : ያንተን ጎን በጦር

በዚያ መንገድማ

አንተን ለማሳመም:  ማን እኔን መሰለ
ስንቴ እንዳቆሰልኩህ … 
ስንቴ እንደወጋሁህ : እኔን ታወቀኝ የለ!

ያ …የጲላጦስ ጭፍራ
በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ
በጦሩ ቢወጋህ ሳያዝን ሳይራራ 
ከቀኝ ጎን አፍስሰህ  ውኃው ከደም ጋራ
በፍቅርህ ስታስረው  ዐይኑን ስታበራ

ትዕግስትህን ጎትቶት   ባንተ እንደ ተጠራ
ምናለ እንደው ’ኔንም …
ላንተ ብቻ እንዲያድር : ልቤን ብታበራ

🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም

ምነው በመሰልኳት
የቺን አመንዝራ
እንደርሷ ላንድ ቀን : ከፊትህ ብጠራ

ለዝሙት አይደለም ነፍሴን ለማሳደፍ
አልያም ለመርከስ መቅደስክን ለማጉደፍ

በዚያ መንገድማ

ነውርን በመሸከም : መች ከእርሷ አንሳለሁ
ሕግህን በማፍረስ …
እኔን ታውቀኝ የለ : ምን እነግርሃለው

ያቺን … ድኩም ዘማ
በኃጢአቷ ቆስላ በበደሏ ታ’ማ
ዓለም ተሰብስቦ ሕይወቷን ሊቀማ
እንዲወግሯት ሳትፈርድ ቸርነትህ ቀድማ
መሬቱን ስትጭር ድምጽህ ሳይሰማ
ነውሯን እንደቀበርክ በከሳሽ ፊት ቆማ

ዳግም አትበድዪ : በፍቅር ሂጂ እንዳልካት
እንደው የኔንም ነፍስ …
ምናለ መልሰህ: እንዲያ በማረካት

🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት

✍️๏ በአግናጥዮስ  🖊 ሕዳር ካህናተ ሰማይ ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፃፈ
☞ ከምድር ጌጥ ታላቋ ደብረ ሊባኖስ

Комментарии

Информация по комментариям в разработке